ሩሲያውያን ታዳጊ የጂምናስቲክ ስፖርተኞች በቢሮክራሲያዊ መዘግየቶች ምክንያት ከ2026 የአውሮፓ ዋንጫ ውጪ ሆኑ
11:39 27.04.2026 (የተሻሻለ: 11:45 27.04.2026)

© Sputnik
ሰብስክራይብ
ሩሲያውያን ታዳጊ የጂምናስቲክ ስፖርተኞች በቢሮክራሲያዊ መዘግየቶች ምክንያት ከ2026 የአውሮፓ ዋንጫ ውጪ ሆኑ
የሩሲያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ለስምንት ስፖርተኞች በ"ገለልተኛ ተወዳዳሪነት" ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ማመልከቻ በመጋቢት ወር አጋማሽ ላይ ያቀረበ ቢሆንም፣ የፍቃድ ሂደቱ እንዲፋጠን በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርብም ምላሽ ያገኘው የምዝገባ ጊዜ ካለፈ እና ዕጣ ማውጣት ከተከናወነ በኋላ ነው።
የአውሮፓ ጂምናስቲክ ስፖርተኞቹ መስፈርቶችን ሁሉ ቢያሟሉም፣ እንዲገቡ አልተፈቀደላቸውም። ይህም ባለፈዉ ዓመት (2025) ታህሳስ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ “የሩሲያ ወይም የቤላሩስ ፓስፖርት ያላቸው ታዳጊ ስፖርተኞች በዓለም አቀፍ የወጣቶች ውድድር ላይ ከእንግዲህ ገደብ ሊጣልባቸው አይገባም” ሲል ካወጣው መግለጫ ጋር የሚጋጭ ሆኗል።
በዓለም አቀፍ እና በአውሮፓ ጂምናስቲክ ማኅበራት በኩል በታየ የአስተዳደር እንቅፋት እና የመዘግየት ሂደት ምክንያት ለወራት የተደረገው ዝግጅት መና ቀርቷል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |
የሩሲያ ጂምናስቲክ ፌዴሬሽን ለስምንት ስፖርተኞች በ"ገለልተኛ ተወዳዳሪነት" ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን ማመልከቻ በመጋቢት ወር አጋማሽ ላይ ያቀረበ ቢሆንም፣ የፍቃድ ሂደቱ እንዲፋጠን በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርብም ምላሽ ያገኘው የምዝገባ ጊዜ ካለፈ እና ዕጣ ማውጣት ከተከናወነ በኋላ ነው።
የአውሮፓ ጂምናስቲክ ስፖርተኞቹ መስፈርቶችን ሁሉ ቢያሟሉም፣ እንዲገቡ አልተፈቀደላቸውም። ይህም ባለፈዉ ዓመት (2025) ታህሳስ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ “የሩሲያ ወይም የቤላሩስ ፓስፖርት ያላቸው ታዳጊ ስፖርተኞች በዓለም አቀፍ የወጣቶች ውድድር ላይ ከእንግዲህ ገደብ ሊጣልባቸው አይገባም” ሲል ካወጣው መግለጫ ጋር የሚጋጭ ሆኗል።
በዓለም አቀፍ እና በአውሮፓ ጂምናስቲክ ማኅበራት በኩል በታየ የአስተዳደር እንቅፋት እና የመዘግየት ሂደት ምክንያት ለወራት የተደረገው ዝግጅት መና ቀርቷል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |