ለአፍሪካ የሚገባት ትርጉም ያላቸው ካሳዎች ምን መምሰል እንዳለባቸው ናይጄሪያዊቷ ባለሥልጣን ያብራራሉ

ሰብስክራይብ
ለአፍሪካ የሚገባት ትርጉም ያላቸው ካሳዎች ምን መምሰል እንዳለባቸው ናይጄሪያዊቷ ባለሥልጣን ያብራራሉ


የናይጄሪያ ብሔራዊ ቤተ-መዘክሮች እና ቅርሶች ኮሚሽን የአስተዳደር ኃላፊ ዋሳ ገርትሩድ ሞቡኑብሃታ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደገለጹት፣ "የባህል ቅርሶቻችን መመለስ ያለ ምንም ገደብ ሊከናወን ይገባል።"


ባለሥልጣኗ በተግባር ሊታዩ ይገባሉ ያሏቸውን እርምጃዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

​🟠 የዕዳ ስረዛ፦ አፍሪካ በራሷ እግር እንዳትቆም እንቅፋት የሆነባትን ዕዳ ሙሉ በሙሉ መሰረዝ፤

​🟠 የተዘረፉ ቅርሶችን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መመለስ፦ በመላው ዓለም በሚገኙ ሙዚየሞች ውስጥ ያሉ የባህል ቅርሶችን ወደ ሀገራቸው መመለስ፤

​🟠 የገንዘብ ድጋፍ፦ ለአፍሪካ ሙዚየሞች፣ ቤተ-መዛግብት፣ ምርምሮች እና የትምህርት ዕድሎች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0