የአፍሪካ ልዑካን በሞስኮ ከዓለም አቀፍ ሶሻሊስቶች ጋር በመሆን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጀግኖችን ዘከሩ

ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ልዑካን በሞስኮ ከዓለም አቀፍ ሶሻሊስቶች ጋር በመሆን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጀግኖችን ዘከሩ

"​የሶቪንተርን" ዓለም አቀፍ የሶሻሊስት ትስስር ፎረም ከመጀመሩ አስቀድሞ፣ ከ70 በላይ ሀገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ ተወካዮች በማይታወቀው ወታደር መቃብር ላይ የአበባ ጉንጉን ማኖራቸውን የትስስሩ ይፋዊ መግለጫ አስታውቋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከተገኙት መካከል፦

ቡከር ንጌሳ ኦሞሌ፦ የኬንያ ኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ፣
ክሪስፒን ካባሴሌ ትሺማንጋ፦ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የዲሞክራቲክ ሶሻሊስቶች ሕብረት ፕሬዝዳንት እና
ሰኢድ ባካሊ፦ የሞሮኮ የዕድገትና ሶሻሊዝም ፓርቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ፀሐፊ።


የሩሲያ ስቴት ዱማ ምክትል ሊቀመንበር አሌክሳንደር ባባኮቭ እንደተናገሩት፣ "እዚህ የተገኘነው በሕይወታቸው መስዋዕትነት የእናት ሀገራቸውን ነፃነትና ሉዓላዊነት ላስከበሩት ክብር ለመስጠት ነው። የሶቪዬት ሕዝቦች የፈጸሙት ገድል በማኅበራዊ ፍትህ እና በዘመናዊ አረመኔነት ላይ የሚታገሉትን ሁሉ አንድ ያደርጋል" ብለዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0