አትሌት ትዕግስት አሰፋ የራሷን ክብረ ወሰን በማሻሻል የለንደን ማራቶንን ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች

አትሌት ትዕግስት አሰፋ የራሷን ክብረ ወሰን በማሻሻል የለንደን ማራቶንን ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች
አትሌት ትዕግስት አሰፋ የራሷን ክብረ ወሰን በማሻሻል የለንደን ማራቶንን ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.04.2026
ሰብስክራይብ
አትሌት ትዕግስት አሰፋ የራሷን ክብረ ወሰን በማሻሻል የለንደን ማራቶንን ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ አሸነፈች

አትሌቷ ውድድሩን በ2:15:41 በመጨረስ በራሷ የተያዘዉን ክብረ ወሰን በዘጠኝ ሰከንዶች በድጋሚ አሻሽላለች።

​ ኬንያዊቷ ሄለን ኦቢሪ በ2:15:53 2ኛ ደረጃን በመያዝ ስታጠናቅቅ፣ ሌላኛዋ ኬኒያዊት ጆይሲሊን ጄፕኮስጌ በተመሳሳይ 2:15:53 በሆነ ሰዓት ተከታትላ ገብታለች

በወንዶች ኬኒያዊዉ ሰባስቲያን ሳዌ ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች የገባ የመጀመሪያው ሰው በመሆን፣ 1:59:30 በመግባት አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።

ኢትዮጵያዊ ዮሚፍ ቀጀልቻ በመጀመሪያ የማራቶን ተሳትፎው፣ አስደናቂ በሆነ 1:59:41 ሰዓት ከ2 ሰዓት በታች በመግባት የኢትዮጵያዊ ክብረ ወሰን ሰብሯል፡፡

እንዲሁም ጃኮብ ኪፕሊሞ 2:00:28 በሆነ ሰዓት በመግባት የቀደመውን የዓለም ክብረ ወሰን አሻሽሏል፡፡

የወንዶች ውጤት ሁለት ሰዎች ከ2 ሰዓት በታች የገቡ ሲሆን ሦስት ሰዎች የዓለም ክብረ ወሰን መስበራቸውን የዓለም አትሌቲክስ ፌድሬሽን አስታውቋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0