'ሕግጋትን የሚያወጡት ለራሳቸው ነው'፤ ናይጄሪያዊቷ ባለሥልጣን ምዕራባውያን የአፍሪካ ቅርሶች እንዳይመለሱ እንዴት እንደሚያግዱ አብራሩ
17:23 26.04.2026 (የተሻሻለ: 18:24 26.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
'ሕግጋትን የሚያወጡት ለራሳቸው ነው'፤ ናይጄሪያዊቷ ባለሥልጣን ምዕራባውያን የአፍሪካ ቅርሶች እንዳይመለሱ እንዴት እንደሚያግዱ አብራሩ
ቅርሶችን "ያለመመለስ" ጉዳይ ፖለቲካዊ ውሳኔ መሆኑን የናይጄሪያ ብሔራዊ ቤተ-መዛክርት እና ቅርሶች ኮሚሽን አስተዳደር ኃላፊ ዋሳ ገርትሩድ ሞቡኑብሃታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፣ ቅርሶችን ለመመለስ እንቅፋት የሆኑ ሦስት ዋና ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
🟠የሀገር ውስጥ የሕግ መሰናክሎች፦ እንደ 'የጎርጎሮሳውያኑ 1963ቱ የብሪቲሽ ሙዚየም ሕግ' ያሉ ደንቦች፣ ቅርሶችን በምንም ዓይነት ሁኔታ መመለስን ይከለክላሉ፡፡
🟠 የ'ሁለንተናዊ ሙዚየም' መከራከሪያ፦ ምዕራባውያን "በታዳጊ ሀገራት ውስጥ ተገቢ የሆነ የመሠረተ ልማት እጥረት አለ" በሚል ሰበብ፣ ቅርሶቹ እኛ ዘንድ መቆየት አለባቸው እያሉ ሁሉንም ሀገራት ይሞግታሉ፡፡
🟠 ወደ ኋላ የማይሠሩ ውሎች፦ እንደ 'የጎርጎሮሳውያኑ 1970 የዩኔስኮ ኮንቬንሽን' ያሉ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች፣ ተፈጻሚ የሚሆኑት ከስምምነቱ ቀን በኋላ በተሰረቁ ዕቃዎች ላይ ብቻ ነው።
"ነገር ግን በእኛ መካከል ምንም ዓይነት መከፋፈል የለም፤ ከንጉሣዊ ቤተ መንግሥቱ ጀምሮ እስከ ሙዚየሞችና እስከ ፌዴራል መንግሥቱ ድረስ እነዚህ ቅርሶች እንዲመለሱ ለማድረግ ጥረታችንን በቅንጅትና በተገቢው መንገድ እያከናወንን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
የቅኝ ግዛት ዘረፋ የአፍሪካን እድገት እንዴት እንዳስተጓጎለ ለመረዳት ቪዲዮውን ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X