‘ልማት የማይጠናቀቅ አጀንዳ ነው’ - የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት
በኢስዋቲኒ ሎባምቤ ውስጥ በተካሄደው የንጉሥ ምስዋቲ ሣልሳዊ የ40ኛ ዓመት የንግሥና በዓል አከባበር ላይ የታደሙት ፕሬዚዳንት ምናንጋጓ፤ "ትልቅም ይሁን ትንሽ፣ ለየትኛውም ሀገር ልማት ፍጻሜ የለውም። ልማት ቀጣይነት ያለው ሂደት ነው" ብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ የጠቀሷቸው ቅድሚያ የሚሰጣቸው ቁልፍ ጉዳዮች፦
🟠 መሠረተ ልማት፦ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን በመንገዶች እና በሕዝብ ግንባታ ሥራዎች ላይ ቀጣይነት ያለው ኢንቨስትመንት ማድረግ፣
🟠 ንግድ፦ ምርቶችን፣ አገልግሎቶችን እና የሰው ኃይልን ጨምሮ በዚምባብዌ እና በኢስዋቲኒ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማሳደግ፣
🟠 እንደ ቆዳ ውጤቶች፣ የመድኃኒት ምርት፣ የቁንጅና መጠበቂያዎች እና አስፈላጊ ዘይቶችን በመሰሉ ዘርፎች ላይ እየታዩ ያሉ ሰፊ እድሎችን መጠቀም።
"እዚህ ተገኝተን የክብረ በዓሉ ምስክር እና አካል እንድንሆን መጋበዛችን ትልቅ ክብር እንደሆነ ይሰማናል። ይህም በዚምባብዌ እና በዚህ መንግሥት (ኢስዋቲኒ) መካከል ያለውን ወንድማማችነት እና ወዳጃዊ ግንኙነት የሚያሳይ በመሆኑ እዚህ በመገኘታችን በጣም ደስተኞች ነን" ብለዋል።
ምሥሉ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X