የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስር ሊቋቋም ነው

የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል
የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 25.04.2026
ሰብስክራይብ
የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስር ሊቋቋም ነው

ዩኒቨርሲቲውና የቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት የጋራ የምርምር ማዕከሉን ለማቋቋም የሚያስችል ስምምነት በትናንትናው ዕለት ተፈራርመዋል።

ዓላማው በቻይና እና በአፍሪካ መካከል ያለውን አካዳሚያዊ ትብብር ማጠናከር፣ የባሕል ልውውጥን ማሳደግ እና የጋራ የምርምር ሥራዎችን ማከናወን መሆኑ ተጠቁሟል።


“ማዕከሉ የሁለቱ ሀገራት ለዓመታት የዘለቀ ጠንካራ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ውጤት ነው” ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ በስምምነት ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ተናግረዋል።


ማዕከሉ በቻይና መንግሥት ከሚደገፉት 25 የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከላት መካከል አንዱ ይሆናል ተብሏል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0