ደቡብ አፍሪካ ወደ ሩሲያ የምትልከውን የወይን ጠጅ ምርት ለማሳደግ ፍላጎት አላት - ፌስኮ

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ ወደ ሩሲያ የምትልከውን የወይን ጠጅ ምርት ለማሳደግ ፍላጎት አላት - ፌስኮ

ትልቁ የሩሲያ የኮንቴይነር ትራንስፖርት ድርጅት "ፌስኮ" ቅርንጫፍ ዳይሬክተር ጆርጂ ረሚዞቭ፤ "ደቡብ አፍሪካ የታሸጉ የወይን ጠጆችን፣ አደገኛ ያልሆኑ ኬሚካሎችን እና የኢንዱስትሪ መሣሪያዎችን ወደ ሩሲያ ለመላክ ፍላጎት አላት" ሲሉ ለስፑትኒክ ገልፀዋል።

ለሩሲያ የችርቻሮ ንግድ ገበያ "ቀጥተኛ የአቅርቦት መስመሮችን በመዘርጋት" የደቡብ አፍሪካ ወይን ጠጆችን በሩሲያ ገበያ በስፋት ለማሰራጨት የሚያስችል አቅም መኖሩን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

እንደ ረሚዞቭ ገለጻ፤ ሩሲያ ወደ ደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ የምትልካቸው ዋና ዋና ምርቶች ብዙም ለውጥ ያልታየባቸው ሲሆን፣ የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

ማዳበሪያ፣

እህል፣

የእንጨት ውጤቶች።

"በሚላኩት የጭነት አይነቶች ላይ ከፍተኛ ለውጥ አልታየም። ለምሳሌ በተለምዶ ሻይ እና ቡና ከኬንያ የሚቀርቡ ምርቶች ናቸው" ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0