ለኮንጎ የተበረከተው የሩሲያ ላቦራቶሪ የበሽታዎች መነሻ (ማዕከል) ድረስ ሄዶ እንዲሠራ ተደርጎ የተነደፈ ነው - የኮንጎ ባዮሎጂስት

ሰብስክራይብ
ለኮንጎ የተበረከተው የሩሲያ ላቦራቶሪ የበሽታዎች መነሻ (ማዕከል) ድረስ ሄዶ እንዲሠራ ተደርጎ የተነደፈ ነው - የኮንጎ ባዮሎጂስት

ይህ ባለ አራት እግር ተሽከርካሪ "ሌሎች ተሽከርካሪዎች መድረስ የማይችሉባቸው ቦታዎች ድረስ መድረስ ይችላል" ሲሉ ዜሬት ኢንዶሎ ጊስሌን በብራዛቪል እየተካሄደ ከሚገኘው ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ዓለም አቀፍ የተላላፊ በሽታዎች መከላከል ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።


አክለውም "ይህ ላቦራቶሪ በየትኛውም የወረርሽኝ መነሻ ወይም ማዕከል ላይ ተገኝቶ እንዲሠራ ተደርጎ የተነደፈ ነው" ብለዋል።


ላቦራቶሪው በፒ3 የመከላከያ አቅሙ ተገቢውን የባዮ-ደህንነት መስፈርት በመጠቀም በጣም አስጊ የኢንፌክሽን አይነቶችን በተሻለ ሁኔታ ለመመርመር ያስችላል።

በላቦራቶሪው ውስጥ የሚሠሩ የኮንጎ ባለሙያዎች በሩሲያ ስፔሻሊስቶች ሥልጠና እንደተሰጣቸው ጊስሌን ተናግረዋል።

ኮንፈረንሱ በሩሲያ የጤና ጥበቃ አገልግሎት "ሮስፖትሬብናድዞር" አዘጋጅነት በብራዛቪል ሲካሄድ ቆይቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0