የሩሲያ ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪዎች ‘በጣም ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን ለመድረስ ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ’ - የብሩንዲ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የሩሲያ ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪዎች ‘በጣም ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን ለመድረስ ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ’ - የብሩንዲ ባለሙያ

በብራዛቪል እየተካሄደ ከሚገኘው ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የተላላፊ በሽታዎች ኮንፈረንስ ጎን ለጎን የብሩንዲ ብሔራዊ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጆሴፍ ኒያንዲዊ፤ "አንዳንድ ጊዜ የጤና ችግሮች በሚከሰቱበት ወቅት ትክክለኛ ምርመራ ለማድረግ በጣም ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን መድረስ ፈታኝ ይሆናል፤ ለዚህም ነው እነዚህ ተንቀሳቃሽ ሥርዓቶች አስፈላጊ የሆኑት" ሲሉ ተናግረዋል።

የሩሲያ ባለሙያዎች ከአፍሪካውያን አጋሮቻቸው ጋር ለመሥራት ያላቸው ዝግጁነት የዚህ ዝግጅት አንዱ "አዎንታዊ ጎን" መሆኑን ጠቁመዋል።

ኒያንዲዊ የኮንፈረንሱን አደረጃጀት በማድነቅ፤ የሚቀጥለው ስብሰባ በሀገራቸው ብሩንዲ እንዲካሄድ ጥያቄ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0