በኬንያ 36 ሰዎችን ያሳፈረ አውሮፕላን ማኮብኮቢያውን ጥሶ ቁጥቋጦ ውስጥ ገባ
19:53 24.04.2026 (የተሻሻለ: 19:54 24.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኬንያ 36 ሰዎችን ያሳፈረ አውሮፕላን ማኮብኮቢያውን ጥሶ ቁጥቋጦ ውስጥ ገባ
ኢቢቢ ኤር በተባለው የኬንያ አየር መንገድ የሚንቀሳቀሰው የኢምብራየር ጄት፤ 32 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሠራተኞችን አሳፍሮ ከናይሮቢ መነሳቱን የኬንያ የአውሮፕላን ማረፊያዎች ባለሥልጣን አስታውቋል።
አውሮፕላኑ በማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ ካረፈ በኋላ ማኮብኮቢያውን ስቶ በመውጣት በአቅራቢያው ወደሚገኝ ቁጥቋጦ ውስጥ ገብቷል።
ባለሥልጣኑ፤ "መንገደኞች እና የበረራ አባላትን በሰላም እንዲወጡ ተደርጎ በአፋጣኝ አስፈላጊው ድጋፍ ቀርቧል። በመንገደኞችም ሆነ በሠራተኞች ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የለም" ብሏል።
ℹ ከሶማሊያ እና ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘው የማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ፤ በዋናነት ለስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የሚላኩ ሰብዓዊ እርዳታዎችን እንዲሁም ለባለሥልጣናት እና ለነጋዴዎች የሚከራዩ በረራዎችን የሚያገለግል ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X