አልጄሪያ እና ቻድ ‘ወደተቀናጀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመሸጋገር’ ወሳኝ እርምጃ ወስደዋል - ፕሬዝዳንት ተቦን

ሰብስክራይብ
አልጄሪያ እና ቻድ ‘ወደተቀናጀ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመሸጋገር’ ወሳኝ እርምጃ ወስደዋል - ፕሬዝዳንት ተቦን

ፕሬዚዳንት አብደልመጂድ ተቦን እና የቻድ አቻቸው መሐማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ በአልጀርስ የተለያዩ ዘርፎችን የሚያካትቱ ወደ 30 የሚጠጉ ስምምነቶች እና የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራርመዋል።

ስምምነቶቹ የሚከተሉትን ዘርፎች ያካትታሉ፦

ኢኮኖሚ እና ንግድ፦ በተለይም ኢነርጂ፣ ማዕድን፣ መሠረተ ልማት እና የመድኃኒት ኢንዱስትሪን ይሸፍናሉ።

የሰው ኃይል ሥልጠና፦ አልጄሪያ “ለበርካታ የቻድ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና ለመስጠት” ቃል መግባቷን ተቦን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ደህንነት እና ሽብርተኝነትን መዋጋት፦ በሳኅል ቀጠና የሚታዩ የጋራ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ቅንጅታዊ አሠራርን መፍጠር።

ሁለቱ መሪዎች ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ “በሱዳን ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ሕጋዊ እና ሰብዓዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ” ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0