ሩሲያ ወረርሽኝ መከላከያ ቴክኖሎጂዎቿን ለአፍሪካ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን የሀገሪቱ የጤና ኤጀንሲ ገለፀ
19:37 22.04.2026 (የተሻሻለ: 19:44 22.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ ወረርሽኝ መከላከያ ቴክኖሎጂዎቿን ለአፍሪካ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን የሀገሪቱ የጤና ኤጀንሲ ገለፀ
የተለመዱት የሰሜኑ የዓለም ክፍል ለጋሾች በሚሊዮን የሚቆጠር እርዳታ ቢሰጡም፤ የአፍሪካን የራስ አቅም መገንባት አልቻሉም ሲሉ የሩሲያ የጤና አጠባበቅ አገልግሎት ኃላፊ አና ፖፖቫ ገልጸዋል።
በኮንጎ እየተካሄደ በሚገኘው ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ሲናገሩ "እርዳታው በቤተ-ሙከራ መሠረተ ልማት እና በአነስተኛ ሥልጠና ላይ ብቻ የተገደበ ነው። ይህ አካሄድ አፍሪካን አይጠቅምም" ብለዋል።
ሩሲያ የወረርሽኝ ስጋቶችን ለመመከት የሚያስችል ልዩ እና የላቀ ልምድ እንዲሁም ቴክኖሎጂዎች ያሏት መሆኑን የገለጹት ፖፖቫ፤ የአፍሪካን ወረርሽኞችን በራስ የመከላከል አቅም ማጠናከር ለቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የባዮሎጂ ደህንነት ቁልፍ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሩሲያ እና አፍሪካ ታሪካዊ የበሽታ መከላከል ትብብር በአመራሮች ቆራጥነት እንደ አዲስ መነቃቃት ማግኘቱንም ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X