ኡጋንዳ የነዳጅ አቅርቦቷ የተረጋጋና የተረጋገጠ እንደሆነ ገለጸች

ሰብስክራይብ

ኡጋንዳ የነዳጅ አቅርቦቷ የተረጋጋና የተረጋገጠ እንደሆነ ገለጸች

የኡጋንዳ የኢነርጂ እና ማዕድን ልማት ሚኒስቴር እንዲሁም ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ የነዳጅ አቅርቦቱ የተረጋጋ እና በጥሩ ሁኔታ እየተመራ መሆኑን ለዜጎች አረጋግጠዋል።

በአሁኑ ወቅት ያለው የነዳጅ ክምችት ሀገራዊ ፍላጎትን ለመሸፈን የሚያስችል ነው፦

ቤንዚን፦ 70.5 ሚሊዮን ሊትር (ለ19 ቀናት የሚበቃ)፣

ናፍጣ፦ 43.2 ሚሊዮን ሊትር (ለ12 ቀናት የሚበቃ)።

በሚቀጥለው ግንቦት ወር የሚገቡ ተጨማሪ የነዳጅ ምርቶች ለቤንዚን የ49 ቀናት፤ ለናፍጣ ደግሞ የ74 ቀናት ሽፋን እንደሚሰጡ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በተጨማሪም ሸማቾችን ከዋጋ ጭማሪ ለመጠበቅ መንግሥት የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ የሚፈጠረውን ዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ መዋዠቅ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን አመልክቷል።

ቪዲዮው ለኡጋንዳ የሚቀርበው ነዳጅ ዋነኛ መሸጋገሪያ የሆነውን የኬንያውን የሞምባሳ ወደብ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0