ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በይፋ ሥራ ጀመረ

ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት
ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.04.2026
ሰብስክራይብ
ተንቀሳቃሽ የመሶብ አገልግሎት በይፋ ሥራ ጀመረ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አገልግሎቱን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል፡፡

አውቶቡሱ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀና ቀልጣፋ አሠራርን የሚያረጋገጥ ነው ተብሏል።

በተንቀሳቃሽ መሶብ የስምንት የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ወሳኝ አገልግሎቶች ተካቷል፦

‎- አዲስየግብር ከፋይ መለያ ቁጥር መስጠት፣
‎- የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ማደስ፣
‎- የመንጃ ፈቃድ የህክምና ምርመራ፣
‎- የነዋሪነት መታወቂያ ማደስና የልደት ምዝገባ፣
‎- መንጃ ፈቃድ መስጠትና የተሽከርካሪ ታርጋ ማደስ፣
‎- የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የመንገድ ፈንድ ክፍያ፣
‎- የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባና የመረጃ እርማት፣
‎- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ አገልግሎቶች።

በተጨማሪም ኢንተርኔትና ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል (8 ኪሎ ዋት የፀሐይ ብርሃን) የሚያገኝበት ስርዓት ተገጥሞለታል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0