የጋዳፊ ውድቀት የኢራን ውሳኔ ሰጪዎችን “ስትራቴጂካዊ አረዳድ ሊገልጥ ይገባል” - ቡርኪናፋሷዊ የፖለቲካ ተንታኝ

ሰብስክራይብ

የጋዳፊ ውድቀት የኢራን ውሳኔ ሰጪዎችን “ስትራቴጂካዊ አረዳድ ሊገልጥ ይገባል” - ቡርኪናፋሷዊ የፖለቲካ ተንታኝ

ምዕራባውያን “ሕግ እንደሚንቁ” እ.ኤ.አ በ2011 ኔቶ በሊቢያ ባደረገው ጣልቃ ገብነት ታይቷል፤ ቴህራንም በማንኛውም ድርድር ወቅት ይህንን ግምት ውስጥ ማስገባት አለባት ሲሉ ሊያንሁዌ ኢምሆቴፕ ባያላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“ኢራን ከምዕራባውያኑ ወገን የሚቀርቡ የድርድር ጥያቄዎችን የመራቅ ሙሉ መብት አላት። ምክንያቱም ይህ ሕግጋትን የሚጥስ ስብስብ ነው። የጋዳፊ ምሳሌ የኢራን ውሳኔ ሰጪዎችን ህሊና እና ስትራቴጂካዊ ግንዛቤ ሊያነቃ ይገባል” ብለዋል።

ከሊቢያ በተለየ መልኩ ኢራን አሊ ካሜኒን በፍጥነት መተካት ያስቻለ “ጠንካራ እና ያልተማከለ የፖለቲካ መዋቅር” እንዳላት ባለሙያው አጽንኦት ሰጥተው አንስተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0