የሱዳን ጦር ለኢትዮጵያ ድንበር ቁልፍ መስመር የሆነችውን የብሉ ናይል ከተማ ሞቅጃን ዳግም ተቆጣጠረ

የሱዳን ጦር
የሱዳን ጦር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.04.2026
ሰብስክራይብ
የሱዳን ጦር ለኢትዮጵያ ድንበር ቁልፍ መስመር የሆነችውን የብሉ ናይል ከተማ ሞቅጃን ዳግም ተቆጣጠረ

ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው የሞቅጃ ከተማ ዳግም ቁጥጥር ስር የዋለችው፤ ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እና ከሱዳን ሕዝባዊ ነፃነት ንቅናቄ-ሰሜን አማፂያን ጋር ከተደረገ ከባድ ውጊያ በኋላ መሆኑን የጦሩ ይፋዊ መግለጫ አመልክቷል።

ከተማዋ በብሉ ናይል ግዛት እና በምስራቃዊው የድንበር ቀጣና መካከል ወሳኝ የሆኑ የአቅርቦት መስመሮችን የምታስተናግድ በመሆኗ፤ ለቀጣይ ወታደራዊ ዘመቻዎች ትልቅ ስትራቴጂካዊ ፋይዳ አላት ተብሏል።

4ኛ የእግረኛ ክፍለ ጦር በሁለት የሚሊሻ ተሽከርካሪዎች እና የሰው ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ያደረሰ ሲሆን ቀጣዩ ኢላማ በኢትዮጵያ ድንበር ላይ የሚገኘው ታሪካዊው የአማፂያን ይዞታ ያቡስ እንደሚሆን የጦር ምንጮች ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0