- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነት፡- የሀገርን ነፃነትና ክብር የማስጠበቅ ተግባር

የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነት፡- የሀገርን ነፃነትና ክብር የማስጠበቅ ተግባር
ሰብስክራይብ
"የሰብአዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ አሁን ላይ ለማንኛውም ሀገር ምርጫ አይደለም፤ በተለይም ስለ ሀገር ክብር፣ ነፃነት እና ሉዓላዊነት ለሚያስብ ሀገር ይህ ጉዳይ የግድ የሚል ተግባር ነው።" ሲሉ የብሄራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፤ በመጀመሪያው ክፍል በአርኪኦሎጂ እና በሰው ልጅ አመጣጥ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የፓሊዮአንትሮፖሎጂ ተመራማሪዎች ከሆኑት ከዶ/ር በርሄ አስፋው እና ከዶ/ር ዮናስ በቀለ ጋር በመካከለኛው አዋሽ ስለተገኙ አዳዲስ የሳይንስ ግኝቶች እንወያያለን። በሁለተኛው ክፍል፤ የአፍሪካን የሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች የመከላከል አቅም እንዲሁም ከውጭ እርዳታ ጥገኝነት የመውጣት አስፈላጊነትን በተመለከተ ከብሄራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም ጋር የነበረንን ቆይታ እናቀርባለን።
በመጨረሻም አፍሪካ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት ተጠቅማ የምግብ ዋስትናዋን እንዴት ማረጋገጥ ትችላለች? በሚሉ ነጥቦች ዙሪያ ከአፍሪካ ህብረት የግብርና እና ምግብ ዋስትና ክፍል ተጠባባቂ ሃላፊ ዶ/ር ጃኔት ኤደሜ እና ከአግራ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶ/ር ይሄነው ዘውዴ ጋር ያደረግነውን ውይይት አካትተናል።

መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ ፕሮግራም ይከታተሉ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0