ዚምባብዌ እና ሩሲያ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ቃል ገቡ
ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ የሥራ ዘመናቸውን ካጠናቀቁት የሩሲያ አምባሳደር ኒኮላይ ክራሲልኒኮቭ ጋር በሀራሬ ባደረጉት የስንብት ውይይት፤ ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ በፖለቲካ እና በጤና ዘርፎች ያላቸውን የቆየ ግንኙነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
አምባሳደሩ በበኩላቸው የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል፦
ሩሲያ በዚምባብዌ በአልማዝ እና በወርቅ ቁፋሮ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች፡፡
በሩሲያ የቴክኒክ ባለሙያዎች የሚታገዙ ሄሊኮፕተሮች በአሁኑ ወቅት ከሀገሪቱ አብራሪዎች እና የህክምና ባለሙያዎች ጋር በመሆን በአገር አቀፍ የአየር አምቡላንስ አገልግሎት ላይ ተሰማርተዋል፡፡
የሳይበር ደህንነት ስልጠና መርሃ ግብር ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ዚምባብዌ በተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ያልሆነ ወንበር በምትይዝበት ወቅት የሁለትዮሽ ትብብሩ ይበልጥ ይጠነክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጹት አምባሳደሩ፤ ምናንጋግዋ በመጪው ጥቅምት ወር በሞስኮ በሚካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ እንደቀረበላቸውም አረጋግጠዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ የሥራ ዘመናቸውን ካጠናቀቁት የሩሲያ አምባሳደር ኒኮላይ ክራሲልኒኮቭ ጋር በሀራሬ ባደረጉት የስንብት ውይይት፤ ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ በፖለቲካ እና በጤና ዘርፎች ያላቸውን የቆየ ግንኙነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
አምባሳደሩ በበኩላቸው የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል፦
ሩሲያ በዚምባብዌ በአልማዝ እና በወርቅ ቁፋሮ ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፈች ትገኛለች፡፡
በሩሲያ የቴክኒክ ባለሙያዎች የሚታገዙ ሄሊኮፕተሮች በአሁኑ ወቅት ከሀገሪቱ አብራሪዎች እና የህክምና ባለሙያዎች ጋር በመሆን በአገር አቀፍ የአየር አምቡላንስ አገልግሎት ላይ ተሰማርተዋል፡፡
የሳይበር ደህንነት ስልጠና መርሃ ግብር ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ዚምባብዌ በተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ያልሆነ ወንበር በምትይዝበት ወቅት የሁለትዮሽ ትብብሩ ይበልጥ ይጠነክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጹት አምባሳደሩ፤ ምናንጋግዋ በመጪው ጥቅምት ወር በሞስኮ በሚካሄደው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ እንደቀረበላቸውም አረጋግጠዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
