ሩሲያ በሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ የሊቢያ ልዑካን ቡድንን ትጠብቃለች - ላቭሮቭ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ በሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ የሊቢያ ልዑካን ቡድንን ትጠብቃለች - ላቭሮቭ

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከሊቢያ አቻቸው ጣህር አል-ባውር ጋር ካደረጉት ድርድር በኋላ የሰጧቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦

🟠 የሩሲያ እና የሊቢያ መንግስታዊ ተቋማት የጋራ ኮሚሽን ስራን ዳግም ለማስጀመር ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

🟠 ሩሲያ በኢራን ጉዳይ ላይ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እንዲቀጥሉ ትጠብቃለች፤ አዎንታዊ ዜናዎችንም ተስፋ ታደርጋለች፡፡ 

🟠 ሩሲያ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ሀገራት እና በኢራን መካከል ያለውን ግንኙነት ለማሻሻል ለማገዝ ዝግጁ ናት፡፡

🟠 ሩሲያ እና ሊቢያ በቤንጋዚ የሩሲያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ለመክፈት ተስማምተዋል፡፡

🟠 ሩሲያ በዩክሬን ቀውስ ላይ ሊቢያ የምታራምደውን አቋም ታደንቃለች፤ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ ሚዛናዊ እና ገለልተኛ አቋም አላቸው፡፡ 

🟠 ሩሲያ እና ሊቢያ በንግድ ጉዳዮች ላይ የሚሠራውን የመንግስታቱ የጋራ ኮሚሽን ሥራ ለመጀመር ተስማምተዋል፡፡ 

🟠 ሊቢያውያን ያለ ውጭ ጣልቃ ገብነት የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ በራሳቸው መወሰን አለባቸው፡፡

🟠 የሊቢያ ብሔራዊ አንድነት መንግስት ልዑካን ቡድን በሞስኮ ከሩሲያ የኢነርጂ ሚኒስትር ጋር ይገናኛል፡፡ 

🟠 የፍልስጤም-እስራኤል ግጭትን ከዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ገለል ለማድረግ የሚደረጉ ሙከራዎች ሌላው እና በጣም አደገኛ ፈንጂዎች ናቸው።

የሊቢያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጣህር አል-ባውር የሰጧቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦

🟠 ሊቢያ በኢራን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ከመጀመሪያው ጀምሮ ያወገዘች ሲሆን በወንድም የባሕረ ሰላጤ ሀገራት ላይ የሚፈጸመውን ጥቃትም አትቀበልም፡፡ 

🟠 ሊቢያ የሰውን ደህንነት ለመጠበቅ እና የኢነርጂ አቅርቦትን አስተማማኝነት ለማረጋገጥ በቀጣናው ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲኖር ትፈልጋለች፡፡ 

🟠 ሊቢያ በፍልስጤም እና በሊባኖስ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ታወግዛለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0