ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የኤሌክትሮቴክኒካል ኮሚሽን በታዳሽ ኃይልና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለመተባበር ተስማሙ
13:26 21.04.2026 (የተሻሻለ: 13:53 21.04.2026)

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያና ዓለም አቀፉ የኤሌክትሮቴክኒካል ኮሚሽን በታዳሽ ኃይልና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ ለመተባበር ተስማሙ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ እንዳለው መኮንን ከዓለም አቀፉ የኤሌክትሮቴክኒካል ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፊሊፔ ሜትዛገር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
በኢትዮጵያ የሚመረቱ የሶላር ፓነሎች፣ ትራንስፎርመሮች እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና በገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ኮሚሽኑ የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ሀገሪቱ በዘርፉ እያከናወነች ያለችውን ሰፊ ሥራ ከግምት በማስገባት፣ በኮሚሽኑ ውስጥ ያላት የተባባሪ አባልነት ደረጃ ወደ ሙሉ አባልነት እንዲያድግ ሚኒስቴሩ ጥያቄ አቅርቧል።
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ የኮሚሽኑን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ ለማስተናገድ ፍላጎት እንዳላት በይፋ ገልጻለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ እንዳለው መኮንን ከዓለም አቀፉ የኤሌክትሮቴክኒካል ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፊሊፔ ሜትዛገር ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
በኢትዮጵያ የሚመረቱ የሶላር ፓነሎች፣ ትራንስፎርመሮች እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና በገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ኮሚሽኑ የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
ሀገሪቱ በዘርፉ እያከናወነች ያለችውን ሰፊ ሥራ ከግምት በማስገባት፣ በኮሚሽኑ ውስጥ ያላት የተባባሪ አባልነት ደረጃ ወደ ሙሉ አባልነት እንዲያድግ ሚኒስቴሩ ጥያቄ አቅርቧል።
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ የኮሚሽኑን ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ ለማስተናገድ ፍላጎት እንዳላት በይፋ ገልጻለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X