በሜክሲኮ ፒራሚድ አካባቢ በተፈጸመ ተኩስ አንድ ቱሪስት ሲገደል ሌሎች በርካቶች ቆሰሉ

ሰብስክራይብ

በሜክሲኮ ፒራሚድ አካባቢ በተፈጸመ ተኩስ አንድ ቱሪስት ሲገደል ሌሎች በርካቶች ቆሰሉ

▪ ተኩሱ የተካሄደው ከሜክሲኮ ሲቲ አቅራቢያ በሚገኘው የቴኦቲዋካን ጥንታዊ የታሪክ ቦታ ውስጥ በሚገኘውና "የጨረቃ ፒራሚድ" ተብሎ በሚጠራው ታዋቂ የመታሰቢያ ሐውልት አካባቢ እኩለ ቀን ላይ ነው።

▪ እንደ ባለሥልጣናቱ ገለጻ ከሆነ፣ አንድ የታጠቀ ግለሰብ በህንጻው አጋማሽ ላይ ከሚገኝ መድረክ ላይ ሆኖ ተኩስ ከከፈተ በኋላ ራሱን ገድሏል።

▪ በሜክሲኮ ግዛት የደህንነት ሚኒስትር መረጃ መሠረት፣ አንድ ካናዳዊ ቱሪስት ሲገደል፤ ሌላ አንድ ካናዳዊ፣ ሁለት ኮሎምቢያውያን እና አንድ ሩሲያዊ በድምሩ አራት ሰዎች ቆስለው ሕክምና ለማግኘት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።

▪ የቴኦቲዋካን ፒራሚዶች በሜክሲኮ ቀዳሚ ከሚባሉ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን፤ ባለፈው ዓመት ብቻ ወደ 722 ሺ የሚጠጉ ጎብኚዎችን አስተናግደዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0