አፍሪካ የጎደላት የፖለቲካ ውህደት እንጂ የኢኮኖሚ ስምምነት ብቻ አይደለም - ሳሚያ ንክሩማህ
19:36 20.04.2026 (የተሻሻለ: 19:44 20.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አፍሪካ የጎደላት የፖለቲካ ውህደት እንጂ የኢኮኖሚ ስምምነት ብቻ አይደለም - ሳሚያ ንክሩማህ
የጋና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት የኩዋሜ ንክሩማህ ልጅ ሳሚያ ንክሩማህ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፣ አኅጉሪቱ የጋራ የፖለቲካ መሠረት ከሌላት የአፍሪካ የኢኮኖሚ መዋቅሮች እና የንግድ ስምምነቶች እውነተኛ ለውጥ ለማምጣት "በጣም ረጅም ጊዜ" ይፈጅባቸዋል።
እንደ አፍሪካ አኅጉር ነፃ የንግድ ቀጣና ያሉ ተነሳሽነቶች "ድንቅ ስምምነቶች" ቢሆኑም፣ ፈጣንና የተቀናጀ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል የፖለቲካ መሠረት ይጎድላቸዋል ሲሉ ሞግተዋል።
"አባታችን እ.ኤ.አ. በ1963 ቁጭ ብለን በፖለቲካዊ ውህደት ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር እንዳለብን መክሮን ነበር" ያሉት ሳሚያ፤ የጋራ የኢኮኖሚ እቅድ፣ የጋራ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና የተዋሃደ ወታደራዊ ኃይል ያለው የአፍሪካ መንግሥታት ፌዴሬሽን እንዲመሠረት ጥሪ አቅርበዋል።
የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማግኘት ቀላሉ መንገድ አፍሪካ "በመተባበር ሀብቷን ማቀናጀት" እና ጥሬ ዕቃን እሴት ሳያክሉ የመላክን የቅኝ ግዛት መዋቅር መስበር እንደሆነ ፖለቲከኛዋ አክለው ገልፀዋል።
"በዚህ ዝቅተኛ የእሴት ሰንሰለት እና ውጤታማ ባልሆነ ሁኔታ ውስጥ እስከቆየን ድረስ ... አሁንም የአእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ሀገራት ሆነን እንቀጥላለን" ሲሉ ያስጠነቀቁ ሲሆን፣ "ይህ አንድነት በአስቸኳይ ያስፈልገናል" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X