ሰባት የአፍሪካ ሀገራት እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2027 በዓመት ከ6% በላይ እድገት እንደሚያስመዘግቡ የዓለም ባንክ ትንበያ አሳየ
16:19 20.04.2026 (የተሻሻለ: 16:26 20.04.2026)

ሰብስክራይብ
ሰባት የአፍሪካ ሀገራት እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2027 በዓመት ከ6% በላይ እድገት እንደሚያስመዘግቡ የዓለም ባንክ ትንበያ አሳየ
የዓለም ባንክ የቅርብ ጊዜው "የአፍሪካ ፐልስ" ሪፖርት፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ. በ2026 እና በ2028 መካከል ጠንካራ ዓመታዊ እድገት ያስመዘግባሉ የሚል ትንበያ አስቀምጧል።
ቅደም ተከተል በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 ፣ 2027 እና 2028ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባሉ ተብለው የሚጠበቁት የሚከተሉት ያካትታሉ፦
ጊኒ - 8.8% (2026)፣ 11.6& (2027) እና 10.7% (2028) በማስመዝገብ ትመራለች። ለዚህም ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርገው ግዙፉ የሲማንዱ የብረት ማዕድን ፕሮጀክት ሲሆን፣ እ.ኤ.አ እስከ 2030 የሀገሪቱን አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርትን በ26 በመቶ ያሳድጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ - 8.0%፣ 6.9% እና 8.4% እድገት እንደምታስመዘግብ የተተነበየላት ሲሆን፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን እና የኢንዱስትሪ ግብዓትን በማሻሻል ለዚህ እድገት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
ኡጋንዳ - 6.8%፣ 8.5% እና 8.1% ኢኮኖሚዋ ያድጋል የተባለ ሲሆን ከነዳጅ ምርት እና በኬንያ በኩል ከሚዘረጋው አዲስ የወጪ ንግድ የድፍድፍ ነዳጅ ማስተላለፊያ ተጠቃሚ ትሆናለች።
ሩዋንዳ - 7.2 በመቶ፣ 7.6 በመቶ እና፣ 7.3 በመቶ እንዲሁም ታንዛኒያ - 6.1ዐ በመቶ፣ 6.4 በመቶ እና 6.5 በመቶ እያስመዘገበች ሲሆን በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እና በኢንዱስትሪ ሽግግር ላይ ያላቸውን ጠንካራ አፈጻጸም ይቀጥላሉ።
ቤኒን - 7.0%፣ 7.2% እና 7.3% ታስመዘግባለች ተብሎ የተተነበየ ሲሆን ከመዋቅራዊ ለውጦች እና ከግሎ-ጂግቤ የኢንዱስትሪ ቀጠና ተጠቃሚ ትሆናለች።
ኒጀር - 6.7%፣ 6.4% እና 6.1% እድገቷ በነዳጅ ምርት (በቀን ከ110 ሺህ በርሜል በላይ) የሚመራ ቢሆንም፣ እድገቱ ከቤኒን ጋር ያለውን የመጓጓዣ ውጥረት በመፍታት ላይ የተመሰረተ ይሆናል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የዓለም ባንክ የቅርብ ጊዜው "የአፍሪካ ፐልስ" ሪፖርት፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት እ.ኤ.አ. በ2026 እና በ2028 መካከል ጠንካራ ዓመታዊ እድገት ያስመዘግባሉ የሚል ትንበያ አስቀምጧል።
ቅደም ተከተል በጎርጎሮሳዊያኑ 2026 ፣ 2027 እና 2028ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባሉ ተብለው የሚጠበቁት የሚከተሉት ያካትታሉ፦
ጊኒ - 8.8% (2026)፣ 11.6& (2027) እና 10.7% (2028) በማስመዝገብ ትመራለች። ለዚህም ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርገው ግዙፉ የሲማንዱ የብረት ማዕድን ፕሮጀክት ሲሆን፣ እ.ኤ.አ እስከ 2030 የሀገሪቱን አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርትን በ26 በመቶ ያሳድጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢትዮጵያ - 8.0%፣ 6.9% እና 8.4% እድገት እንደምታስመዘግብ የተተነበየላት ሲሆን፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን እና የኢንዱስትሪ ግብዓትን በማሻሻል ለዚህ እድገት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።
ኡጋንዳ - 6.8%፣ 8.5% እና 8.1% ኢኮኖሚዋ ያድጋል የተባለ ሲሆን ከነዳጅ ምርት እና በኬንያ በኩል ከሚዘረጋው አዲስ የወጪ ንግድ የድፍድፍ ነዳጅ ማስተላለፊያ ተጠቃሚ ትሆናለች።
ሩዋንዳ - 7.2 በመቶ፣ 7.6 በመቶ እና፣ 7.3 በመቶ እንዲሁም ታንዛኒያ - 6.1ዐ በመቶ፣ 6.4 በመቶ እና 6.5 በመቶ እያስመዘገበች ሲሆን በግብርና፣ በአገልግሎት ዘርፍ እና በኢንዱስትሪ ሽግግር ላይ ያላቸውን ጠንካራ አፈጻጸም ይቀጥላሉ።
ቤኒን - 7.0%፣ 7.2% እና 7.3% ታስመዘግባለች ተብሎ የተተነበየ ሲሆን ከመዋቅራዊ ለውጦች እና ከግሎ-ጂግቤ የኢንዱስትሪ ቀጠና ተጠቃሚ ትሆናለች።
ኒጀር - 6.7%፣ 6.4% እና 6.1% እድገቷ በነዳጅ ምርት (በቀን ከ110 ሺህ በርሜል በላይ) የሚመራ ቢሆንም፣ እድገቱ ከቤኒን ጋር ያለውን የመጓጓዣ ውጥረት በመፍታት ላይ የተመሰረተ ይሆናል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X