የኒጀሩ መሪ በተኩስ ልምምድ ላይ ተሳተፉ
አብዱራሃማኔ ቲያኒ "በብሔራዊ የህዝብ ደህንነት ኮሚቴ" በተዘጋጀ የተኩስ ልምምድ ላይ ተሳትፈዋል።
በብሔራዊ ኮሚቴው በተጋሩ ምስሎች ላይ እንደታየው፣ መርሃ ግብሩ ሽጉጥ እና ኤኬ-47 ካላሽንኮቭን ጨምሮ በተለያዩ የጦር መሣሪያዎች የታገዘ የትክክለኛ (የኢላማ) ተኩስ ልምምድን ያካተተ ነበር።
ቲያኒ ልምምዱን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩን እና የጦር ኃይሉን ኢታማዦር ሹም ጨምሮ ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን በቁም፣ በበርከክ እና በደረት በመተኛት አቀማመጦች አከናውነዋል።
እንደ ብሔራዊ ኮሚቴው ገለጻ፤ መሰል ልምምዶች አሁን ላይ እንደ “ባህል” እየተለመዱ መጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X