የኒጀሩ መሪ በተኩስ ልምምድ ላይ ተሳተፉ

ሰብስክራይብ

የኒጀሩ መሪ በተኩስ ልምምድ ላይ ተሳተፉ

​አብዱራሃማኔ ቲያኒ "በብሔራዊ የህዝብ ደህንነት ኮሚቴ" በተዘጋጀ የተኩስ ልምምድ ላይ ተሳትፈዋል።

​በብሔራዊ ኮሚቴው በተጋሩ ምስሎች ላይ እንደታየው፣ መርሃ ግብሩ ሽጉጥ እና ኤኬ-47 ካላሽንኮቭን ጨምሮ በተለያዩ የጦር መሣሪያዎች የታገዘ የትክክለኛ (የኢላማ) ተኩስ ልምምድን ያካተተ ነበር።

​ቲያኒ ልምምዱን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩን እና የጦር ኃይሉን ኢታማዦር ሹም ጨምሮ ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን በቁም፣ በበርከክ እና በደረት በመተኛት አቀማመጦች አከናውነዋል።

​እንደ ብሔራዊ ኮሚቴው ገለጻ፤ መሰል ልምምዶች አሁን ላይ እንደ “ባህል” እየተለመዱ መጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0