የሲሼልስ ፕሬዝዳንት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሩሲያ ገቡ
13:23 20.04.2026 (የተሻሻለ: 13:24 20.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሲሼልስ ፕሬዝዳንት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሩሲያ ገቡ
ፕሬዝዳንት ፓትሪክ ሄርሚኒ ሞስኮ አየር ማረፊያ ሲደርሱ፣ በሩሲያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆርጂ ቦሪሴንኮ እና በዲፕሎማቲክ ቡድን አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ከፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መግለጫ እንደሚያመለክተው፣ ይህ ጉብኝት "ሲሼልስ ከሩሲያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እና ብሔራዊ ጥቅሟን ባከበረ መልኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተሳትፎ ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል።"
ውይይቱ በሚከተሉት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፦
🟠 የቱሪዝም ልማት፣
🟠 የኢንቨስትመንት ማበረታቻ፣
🟠 የአየር ትራንስፖርት ትስስርን ማስፋፋት እና
🟠 የምግብ ዋስትና።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X