የአሜሪካ ባህር ኃይል በኦማን ባህረ ሰላጤ በኢራን የጭነት መርከብ ላይ ተኩስ በመክፈት መርከቧን ተቆጣጠረ፤ ኢራን የአጸፋ እርምጃ ለመውሰድ ዝታለች

ሰብስክራይብ

የአሜሪካ ባህር ኃይል በኦማን ባህረ ሰላጤ በኢራን የጭነት መርከብ ላይ ተኩስ በመክፈት መርከቧን ተቆጣጠረ፤ ኢራን የአጸፋ እርምጃ ለመውሰድ ዝታለች

​ ዶናልድ ትራምፕ ትናንት በማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት፤ የአሜሪካ ባህር ኃይል በኦማን ባህረ ሰላጤ በኢራን ሰንደቅ ዓላማ በሚጓዘው ቱስካ በተሰኘው የጭነት መርከብ ላይ ተኩስ መክፈቱን አስታውቀዋል። መርከቧ በአሜሪካ የግምጃ ቤት ማዕቀብ የተጣለባት ኢላማ ነበረች።

​ ኢራን ለመርከቧ መያዝ ፈጣን ምላሽ እንደምትሰጥ የዛተች ሲሆን፣ የሀገሪቱ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሳለች ሲሉ ከሰዋል።

​ የማዕከላዊ እዝ የአሜሪካ ባህር ኃይል የኢራንን የጭነት መርከብ ቱስካ በቁጥጥሩ ስር ሲያውል የሚያሳይ ቪዲዮ በኤክስ ገጹ ላይ ለቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0