'የበላይነት አስተሳሰብ ለሕገወጥ የወረራ ጥቃት እና ለዘር ማጥፋት ዋነኛው መንስኤ ነው' - ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ

ሰብስክራይብ
'የበላይነት አስተሳሰብ ለሕገወጥ የወረራ ጥቃት እና ለዘር ማጥፋት ዋነኛው መንስኤ ነው' - ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ

​በባርሴሎና በተካሄደው የዓለም አቀፍ "ፕሮግረሲቭ ሞቢላይዜሽን" መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት ሲሪል ራማፎሳ፣ እንደ ፍልስጤም ባሉ ቦታዎች ለሚታዩት ዳግም ያገረሹ የጥቃት ጦርነቶች እና የዘር ማጥፋት ድርጊቶች ዋነኛው መንስኤ የበላይነት አስተሳሰብ ነው።


​"ደቡብ አፍሪካ የእስራኤልን መንግስት ወደ ዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ለመውሰድ የመሪነቱን ሚና የተጫወተችው ይህንን የበላይነት የመፈለግ አስተሳሰብ ለመገዳደር ነው። ይህን ስናደርግ ተነቅፈናል፣ ተቃውሞ ገጥሞናል፣ አልፎ ተርፎም ተሰድበናል፤ ነገር ግን በፅናት ቆመናል" ብለዋል።


ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ይህ ወቅት ዓለም አቀፍ ቅስቀሳ የሚደረግበት፣ የታዳሽነት እና የዓለም አቀፋዊ የለውጥ ኃይሎች ዳግም የሚነሱበት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።


​"በፅናት የቆምንበት ምክንያት የዲሞክራሲያችን አባት እንዳለን፣ 'እኛ ደቡብ አፍሪካውያን ያለን ነፃነት፣ ፍልስጤማውያን የራሳቸውን ነፃነት እስካላገኙ ድረስ ሙሉ ሊሆን አይችልም' በማለታቸው ነው" ሲሉ ተናግረዋል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0