የሀሮ ደንዲ ሎጅ፦ “የኢትዮጵያ አዲስ ገጽታ ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ
የሀሮ ደንዲ ሎጅ፦ “የኢትዮጵያ አዲስ ገጽታ ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው እና የ”ገበታ ለትውልድ” መርሃግብር አካል የሆነው የሀሮ ደንዲ ሎጅ በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በይፋ ተመርቋል።

የሎጁ ዋና ዋና ገጽታዎች፦

ግንባታው የተፈጥሮ ሥነ-ምኅዳሩን በመጠበቅ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተርፍ ታስቦ ተከናውኗል።

የደንዲ ክሬተር ሐይቅን ነባራዊ ውበት ሳይነካ፣ ዘመናዊ ሥነ-ሕንጻ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ ተገንብቷል።

የአካባቢውን ማኅበረሰብ ባህላዊ እሴት ባከበረ እና ህዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ተሠርቷል።


‎”የሀሮ ደንዲ ሎጅ፣ የገባነውን ቃል ፈጽመን የመገኘታችን ተጨማሪ ማረጋገጫ ነው። ሎጅው እና የአካባቢው አስደናቂ ሥነ-ምሕዳር ኢትዮጵያን ለመጎብኘት፣ ለኢንቨስትመንት እና ለሁነት ቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ያደርጋታል።” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ሚዲያ አጋርተዋል፡፡


ቪዲዮ፦ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0