'ደቡባዊው ዓለም ላልጀመረው ጦርነት ዋጋ እየከፈለ ነው' – የብራዚል ፕሬዝዳንት

ሰብስክራይብ
'ደቡባዊው ዓለም ላልጀመረው ጦርነት ዋጋ እየከፈለ ነው' – የብራዚል ፕሬዝዳንት

በስፔን ባርሴሎና በተካሄደው 1ኛው የ"ፕሮግረሲቭ ሞቢላይዜሽን" ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉት ሉላ ዳ ሲልቫ፣ በአሜሪካ የበላይነት የሚመራውን የዓለም ስርዓት እና በደቡባዊ ዓለም ላይ እያሳደረ ያለውን ተጽዕኖ ተችተዋል። ፕሬዝዳንቱ ደቡባዊ ዓለም "እንደ ኃያላን ሀገራት የጓሮ መጫወቻ" እየታየ መሆኑን ገልጸዋል።


"የጦር አበጋዞች በሴቶች እና በሕፃናት ላይ ቦምብ ሲጥሉ" ለረሃብ፣ ለኢነርጂ እና ለጤና ችግሮች እልባት ከመስጠት ይልቅ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለጦር መሣሪያ ግዢ እየባከነ መሆኑን ሉላ በንግግራቸው ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ሉላ፣ የተባበሩት መንግሥታት ተዓማኒነት መልሶ እንዲገነባ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ የአደጉ እና በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት በእኩል የሚታዩበት ሥርዓት እንዲዘረጋም ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0