በግብፅ ብርቅዬ የግሪክ እና የሮማውያን ዘመን ቅርሶች ተገኙ - የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚኒስቴር
19:42 18.04.2026 (የተሻሻለ: 19:44 18.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በግብፅ ብርቅዬ የግሪክ እና የሮማውያን ዘመን ቅርሶች ተገኙ - የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚኒስቴር
ግኝቱ በምንያ ግዛት በቅርቡ ለተመዘገቡት ተከታታይ ታላላቅ የአርኪኦሎጂ ግኝቶች ተጨማሪ መሆኑንና የግብፅን ስልጣኔ ብልጽግና እና ብዝሃነት የሚያጎላ መሆኑን የቱሪዝም እና የጥንታዊ ቅርሶች ሚኒስትር ሸሪፍ ፋቲ ገልጸዋል።
ቅርሶቹ የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
▶አንዳንድ በጥበብ በተሰሩ ጨርቃጨርቆች እንደተጠቀለሉ ያሉ ሙሚዎች (በሬሳ ማድረቂያ የቆዩ በድኖች)፤
▶ ደመቅ ያሉ ቀለማት ያሏቸው ከእንጨት የተሰሩ ሬሳ ሳጥኖች፤
▶በአፍ ውስጥ ወይም አጠገብ የተቀመጡ ሦስት የወርቅ እና አንድ የነሐስ ምላሶች፤
▶የተቃጠሉ ቅሪቶች እና የእንስሳት አጥንቶች ያሉባቸው ማሰሮዎች የያዙ ከኖራ ድንጋይ የተሰሩ የመቃብር ክፍሎች፤
▶ ከሸክላ እና ከነሐስ የተሰሩ ምስሎች፣ ሀርፖክራተስን እና ትንሽ የኩፒድ ሃውልትን ያካትታሉ።
ግኝቱ በግሪክ እና በሮማውያን ዘመን በአል-በሃንሳ ከተማ የነበሩ የቀብር ሥነ-ሥርዓቶችን በተመለከተ አዲስ እውቀት የሚሰጥ መሆኑን የጥንታዊ ቅርሶች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ሂሻም ሊቲ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X