በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ የሚገኝ የዝሆን መንጋ የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠበት ተገለፀ

ሰብስክራይብ
በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ የሚገኝ የዝሆን መንጋ የመጥፋት አደጋ እንደተጋረጠበት ተገለፀ

​በመጠለያ ውስጥ የሚገኙ የዝሆኖች ቁጥር ከ13 ዓመታት በፊት 1,000 ከነበረበት አሁን ላይ ወደ 215 ዝቅ ማለቱን የመጠለያው ተወካይ ጠቅሶ የውጭ ሚዲያ ዘግቧል።

ሕገ-ወጥ አደን፣ በመጠለያው ውስጥ የሚመሰረቱ አዳዲስ ሰፈራዎች፣ የደህንነት ችግሮች፣ የደን መጨፍጨፍ፣ የማዕድን ቁፋሮ እና የግጦሽ መሬት ለዝሆኖቹ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደ ዋና ምክንያቶች ተጠቅሰዋል።

​የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ኃላፊን የጠቀሰው ዘገባው፣ ሕገ-ወጥ አደንን እና የዱር እንስሳት ዝውውርን ለመቆጣጠር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጽፏል።

​እ.ኤ.አ. በ1978 የተመሠረተው የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ 6,982 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት የሚሸፍን ሲሆን፣ የ231 የአእዋፍ እና የ31 አጥቢ እንስሳት ዝርያዎች መገኛም መሆኑን መተገልጿ።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ ቪዲዮ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0