ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በምርት ገበያ የንግድ ልውውጥ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ

የንግድ ልውውጥ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ
 የንግድ ልውውጥ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.04.2026
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በምርት ገበያ የንግድ ልውውጥ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ

የሩሲያው ሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ የሸቀጦች የልውውጥ ገበያ ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ጋር አብሮ መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ከድርጅቱ ፕሬዝዳንት ኢጎር አርቴሚየቭ ጋር የሥራ ውይይት ማድረጋቸውን ኤምባሲው አስታውቋል።

​አምባሳደር ገነት በበኩላቸው በኢኮኖሚው ዘርፍ ጠንካራ ትብብር ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት የሰጡ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የንግድ ማኅበረሰብ የገበያ መሠረተ ልማቱን በመጠቀም ወደ ሩሲያ ገበያ በቀጥታ መግባት የሚችልበትን ዕድል ለመፍጠር ተግባራዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ አቅርበዋል።

​አርቴሚየቭ በበኩላቸው፣ ለሁለቱም ሀገራት ኩባንያዎች ቀጥተኛ የገበያ ትስስር መፍጠር፣ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን የሚቀንስ፣ ግልጽነትን የሚያሰፍን እንዲሁም ደህንነቱ የተጠበቀ እና አስተማማኝ የንግድ መስመር መፍጠር እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0