የአሜሪካንን ኢምፔሪያሊዝም ለመዋጋት "እንደ ኢብራሂም ትራኦሬ ያሉ መሪዎችን አርአያ መከተል አለብን" - የዚምባብዌ ፖለቲከኛ

ሰብስክራይብ

የአሜሪካንን ኢምፔሪያሊዝም ለመዋጋት "እንደ ኢብራሂም ትራኦሬ ያሉ መሪዎችን አርአያ መከተል አለብን" - የዚምባብዌ ፖለቲከኛ

​"የቡርኪና ፋሶ ሕዝቦች የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊስቶችን ማስወጣት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራቸውን በራሳቸው ሀብት እያለሙ ይገኛሉ። ከመላው አፍሪካ የሚጠበቀውም ይህ ነው፤ ከሀገር ሀገር ልንከተለው የሚገባ ተግባር ነው" ሲሉ የዚምባብዌ ኮሙኒስት ፓርቲ ዓለም አቀፍ ፀሐፊ ኢያን ቤዶውስ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የኩባ ደጋፊዎች ሰልፍ ላይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

​ቤዶውስ አጽንኦት ሰጥተው እንደገለጹት፣ የአፍሪካ ሀገራት በምድራቸውም ላይ የሚገኙትን የአሜሪካ እና የፈረንሳይ ጦር ሰፈሮችን በሙሉ በማስወገድ "የኩዋሜ ንክሩማህን የፓን-አፍሪካኒዝም ራዕይ" ማለትም "ከኬፕ ታውን እስከ ካይሮ የተባበረች አፍሪካን" መገንባት አለባቸው።

​" የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በእውነትም እየተዳከመ ነው። የብሪክስን ጥንካሬ ካየን፣ ሰዎች የአሜሪካንን ዶላር እየተዉት ነው" ያሉ ሲሆን፤ አሜሪካ ይህንን ውድቀት በኃይል ለመመከት እየሞከረች መሆኑንና ለዚህም በፍልስጤም ያለውን ሁኔታ እንደ ምሳሌ ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0