'ጋምቢያ እና ሩሲያ የቆየ ታሪክ አላቸው' — ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

'ጋምቢያ እና ሩሲያ የቆየ ታሪክ አላቸው' — ሚኒስትር

በቅርቡ በሞስኮ የጋምቢያ ኤምባሲ መከፈቱ እና በባንጁል ደግሞ የሩሲያን ኤምባሲ ለመክፈት የሚደረገው ዝግጅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ያጠናክረዋል ሲሉ የጋምቢያ የመረጃ፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የብሮድካስት አገልግሎት ሚኒስትር ኢስማኢላ ሲሴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም "በሩሲያ የተማሩ በርካታ ጋምቢያውያን አሉን። በተጨማሪም ከድህረ-ቅኝ አገዛዝ ዘመን ጀምሮ ሩሲያ ለጋምቢያ የምታደርገው ከፍተኛ ድጋፍ አለ። ስለዚህ ይህንን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር ጠቃሚ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ከ17ኛው የአፍሪካ ብሮድካስቲንግ ሕብረት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን ገልፀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0