ዛንዚባር በሁሉም የመንግሥት ሆስፒታሎች 100 በመቶ የመድኃኒት ተደራሽነትን ለማሳካት እንደምትሠራ አረጋገጠች

ሰብስክራይብ

ዛንዚባር በሁሉም የመንግሥት ሆስፒታሎች 100 በመቶ የመድኃኒት ተደራሽነትን ለማሳካት እንደምትሠራ አረጋገጠች

የዛንዚባር የጤና ሚኒስትር ሳዳ ምኩያ 15ኛው የጤና ዘርፍ ክለሳ ስብሰባ መክፈቻ ላይ ትልቅ የጤና ማሻሻያ ይፋ አድርገዋል። የመድኃኒት በጀትን በእጥፍ በማሳደግ በ2023/24 ከነበረበት 7.8 ሚሊዮን ዶላር በ2024/25 ወደ 14 ሚሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል ተደርጓል።

ሚኒስትሯ በመንግሥት ሆስፒታሎች ያለውን የመድኃኒት አቅርቦት ከ82.4 በመቶ ወደ 100 በመቶ ለማድረስ ቃል ገብተዋል። ይህም "ማንኛውም ሆስፒታል የሚመጣ ታካሚ አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶችን ሁሉ እንዲያገኝ" ለማስቻል ነው።

አሁንም ትልቅ ፈተና ሆኖ ስለቀጠለው የሰው ኃይል እጥረት ሲገልጹ፤ በየደረጃው በተደረገ ግምገማ የ3,574 የጤና ባለሙያዎች እጥረት መኖሩ ተለይቷል። መንግሥትም ይህንን ክፍተት በቀጣይ የቅጥር መርኃ-ግብሮች ለመሙላት ያቀደ ሲሆን በዘርፉ ከ1,500 በላይ ክፍት የሥራ መደቦች በቅርቡ ማስታወቂያ እንደሚወጣላቸው ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0