ማዳጋስካር 919 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የሕዝብ ሀብት ምዝበራ ላይ ምርመራ እያካሄደች መሆኑ ተገለፀ

ሰብስክራይብ

ማዳጋስካር 919 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የሕዝብ ሀብት ምዝበራ ላይ ምርመራ እያካሄደች መሆኑ ተገለፀ

ለአምስት ዓመታት የዘለቀው ይህ የምዝበራ ድርጊት 15 ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን እና የከተማ ባቡር እንዲሁም የኬብል ተሽከርካሪ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ ዋና ዋና የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ያካተተ እንደሆነ፤ የፕሬዝዳንታዊ ቃል አቀባይ ሃሪ ላውረንት ረሃጃሰንን ጠቅሰው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ፕሬዝዳንት ራንድሪያኒሪና የፀረ-ሙስና ቢሮው ምርመራ እንዲያደርግና ጉዳዮቹን ለዐቃቤ ሕግ እንዲያስተላልፍ ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ማስረጃ እስከተገኘ ድረስ ምንም ዓይነት የሥልጣን ደረጃ ላይ ቢገኝ ማንኛውም ተጠያቂ ግለሰብ ለሕግ እንደሚቀርብ መናገራቸው ተገልጿል።

ባለሥልጣናት በኦዲት ምርመራው እና በፕሬዚዳንት ራንድሪያኒሪና ሕይወት ላይ በተቃጡ ስጋቶች መካከል ሊኖር የሚችለውን ግንኙነት እየመረመሩ እንደሆነ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

ዛሬ ሐሙስ በፕሬዚዳንቱ መኖሪያ ቤት ያልታወቁ ድሮኖች መታየታቸውን ተከትሎ የፀጥታ ኃይሎች በረራውን የግድያ ሙከራ ሲሉ ፈርጀውታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0