‘ታሪክህን ራስህ ካልተናገርክ፤ ሌላ ሰው ይነግርልሃል’ - የጋምቢያ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

‘ታሪክህን ራስህ ካልተናገርክ፤ ሌላ ሰው ይነግርልሃል’ - የጋምቢያ ሚኒስትር

የአፍሪካ ሀገራት እየተስፋፋ የመጣውን የተሳሳተና የሀሰተኛ መረጃ ስጋት በጋራ ሊጋፈጡ እንደሚገባ የጋምቢያ የመረጃ፣ ሚዲያ እና ብሮድካስቲንግ አገልግሎት ሚኒስትር እስማኤላ ሲሴይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ በ17ኛው የአፍሪካ ብሮድካስቲንግ ሕብረት ጠቅላላ ጉባኤ ጎን ለጎን በሰጡት ቃል "ዛሬ ሉዓላዊነታችን አደጋ ላይ ነው። ወደ ሀገርህ ስለሚገባው መረጃ ከአሁን በኋላ ምንም አይነት ቁጥጥር የለህም" ብለዋል።

እስማኤላ ሲሴይ በተጨማሪም የአፍሪካ ሚዲያዎች ለአፍሪካዊ ዜናዎች ሰፊ ሽፋን እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

"አቅማችንን መገንባት፣ የመሠረተ ልማት አውታሮቻችንን ማጠናከር፣ የሚዲያ ምህዳራችንን መደገፍ እና የራሳችንን ይዘት መፍጠር መቻላችንን ማረጋገጥ አስፈላጊ ይመስለኛል" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0