በኢትዮጵያ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑ ጤና ጣቢያዎችና ኬላዎች ዲጂታላይዝ መደረጋቸው ተገለፀ

ሰብስክራይብ

በኢትዮጵያ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑ ጤና ጣቢያዎችና ኬላዎች ዲጂታላይዝ መደረጋቸው ተገለፀ

በሀገሪቱ ገጠራማ አካባቢዎች ከሚገኙ 17 ሺህ በላይ ጤና ጣቢያዎችና ኬላዎች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በዲጂታል የጤና መረጃ ሥርዓት መታቀፋቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ፤ “በዲጂታል ሥርዓቱ እስካሁን ከ30 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች የጤና መረጃ መያዝ ተችሏል” ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።

በቀጣይ 4 ሺህ 500 ሆስፒታሎችንና የጤና ኮሌጆችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተሠራ ሲሆን ይህም "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ን ለማሳካት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0