ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በዓለም አቀፍ የዋጋ ተመኖች ላይ የላቀ ቁጥጥር ለማድረግ ስትራቴጂካዊ የኮባልት ክምችት አቋቋመች

ሰብስክራይብ

ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በዓለም አቀፍ የዋጋ ተመኖች ላይ የላቀ ቁጥጥር ለማድረግ ስትራቴጂካዊ የኮባልት ክምችት አቋቋመች

የሀገሪቱ ካቢኔ "የስትራቴጂካዊ ማዕድናት ቁጥጥር ባለሥልጣን" አዲስ የኮባልት ክምችት እንዲያደራጅ በቅርቡ መመሪያ ሰጥቷል። ይህም ከዚህ ቀደም በኮባልት ምርት መጠን ላይ ከተጣለው ገደብ በተጨማሪ በገበያው ላይ ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚያስችል ሌላ የንግድ መሣሪያ እንደሚሆን የአካባቢው የማዕድን ተቆጣጣሪ ተቋም ገልጿል።

ኮንጎ በዓለም አቀፍ ደረጃ 70 በመቶ የሚሆነውን የኮባልት ምርት በማቅረብ ቀዳሚ ሀገር ስትሆን፤ የኤክስፖርት እገዳዎችን እና የምርት ገደቦችን በመጣሏ ምክንያት የ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ወጪ ምርቷን ወደ 48,800 ቶን ቀንሳለች። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት (123,000 ቶን) ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ የታየበት ነው።

በአዲሱ ሥርዓት መሠረት፤ ከወጪ ምርቱ ውስጥ 10 በመቶ የሚሆነው (9,600 ቶን) ለመንግሥት ስትራቴጂካዊ አገልግሎት እንዲውል ተለይቶ ይቀመጣል።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ ቪዲዮ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0