ኡጋንዳ የውጭ ተፅዕኖን በመገደብ ሉዓላዊነትን የሚያጠናከር አዲስ ረቂቅ አዋጅ አስተዋወቀች

ኡጋንዳ
ኡጋንዳ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.04.2026
ሰብስክራይብ
ኡጋንዳ የውጭ ተፅዕኖን በመገደብ ሉዓላዊነትን የሚያጠናከር አዲስ ረቂቅ አዋጅ አስተዋወቀች

የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዴቪድ ሙሆዚ፤ የ2026ቱ የሉዓላዊነት ጥበቃ ረቂቅ አዋጅ ኡጋንዳ ውስጥ የውጭ ሀገራትን ፍላጎት የሚያስፈጽሙ ግለሰቦችን እና ተቋማትን ለመከታተልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ እንደሚፈጥር ገልፀዋል።

የክትትል ሥራው የሰላም እና ደህንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊነት ሲሆን "የውጭ ሀገር ወኪሎችን" የመመዝገብ እና የመቆጣጠር ሥልጣን ይኖረዋል።

የቀረበው ረቂቅ ሕግ፤ ባለሥልጣናት "የኡጋንዳን ሉዓላዊነት፣ ደህንነት እና አስተዳደር ስጋት ላይ ይጥላሉ" የሚሏቸውን ሕገ-ወጥ ወይም ያልተገለጹ የውጭ የገንዘብ ድጋፎችን እና ለወኪሎቹ የሚሰጡ ሌሎች እርዳታዎችን ኢላማ ያደርጋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0