ላይቤሪያ የኢትዮጵያን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ተሞክሮ በአርአያነት እንደምትወስድ አስታወቀች

ሰብስክራይብ
ላይቤሪያ የኢትዮጵያን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ተሞክሮ በአርአያነት እንደምትወስድ አስታወቀች

ኢትዮጵያ በሰው ሠራሽ አስተውህሎት ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ማሳያ መሆኑን የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳራ ቤይሶሎ ኒያንቲ ተናግረዋል።

በሚኒስትሯ የተመራ የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ የሚገኘውን የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ማክሰኞ ጎብኝቷል።


"የተሻለች ላይቤሪያን ለመገንባት የኢትዮጵያን ምርጥ ተሞክሮዎች እንደ መነሻ እንወስዳለን" ሲሉ ሚኒስትሯ ገልፀዋል።


የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና፤ ኢንስቲትዩቱ ያካበተውን የቴክኖሎጂ እውቀት ለሌሎች አፍሪካውያን ወንድሞች ለማካፈል ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0