ደቡብ አፍሪካ በቅኝ ግዛት ዘመን የተሰረቀውን ቅዱስ የቻፑንጉ ወፍ ለዚምባብዌ መለሰች

ደቡብ አፍሪካ፣ ዚምባብዌ
ደቡብ አፍሪካ፣ ዚምባብዌ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.04.2026
ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ በቅኝ ግዛት ዘመን የተሰረቀውን ቅዱስ የቻፑንጉ ወፍ ለዚምባብዌ መለሰች

ደቡብ አፍሪካ በቅኝ ግዛት ዘመን ለምርምር ዓላማ የተወሰዱትን የስምንት ዚምባብዌያውያን አስከሬንም መልሳለች ሲል የስፖርት፣ የሥነ-ጥበብ እና የባሕል ሚኒስቴር አስታውቋል።


"የእኛ ያልሆነውን መመለስ አለብን" ሲሉ የደቡብ አፍሪካ የስፖርት፣ የሥነ-ጥበብ እና የባሕል ሚኒስትር ጌይተን ማኬንዚ በኬፕ ታውን በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።


ለዚምባብዌያውያን የቅዱስ ምልክት የሆነው የድንጋይ ቅርጽ የቻፑንጉ ወፍ፤ ከ137 ዓመታት በፊት ነበር ከታላቋ ዚምባብዌ ፍርስራሾች የተሰረቀው።

በአካባቢው እምነት መሠረት፤ የቻፑንጉ ወፍ የአማልክትና የቅድመ አያቶች መልዕክቶች አቀባይ እና ሲበር ማየት የመልካም ዕድል ምልክት ተደርጎ ይቆጠራል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0