ሩሲያ ወደ ሱዳን የምትልከውን የስንዴ ምርት በሁለት እጥፍ በማሳደግ 1.7 ሚሊዮን ቶን አደረሰች

ሰብስክራይብ

ሩሲያ ወደ ሱዳን የምትልከውን የስንዴ ምርት በሁለት እጥፍ በማሳደግ 1.7 ሚሊዮን ቶን አደረሰች

የሩሲያው አግሮኤክስፖርት ፌዴራል ማዕከል እንደገለጸው፤ ይህ አፈፃጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ0.7 ሚሊዮን ቶን ወደ 1.7 ሚሊዮን ቶን ጭማሪ አሳይቷል።

በሌላ በኩል የሱዳን ማዕከላዊ ባንክ መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የሀገሪቱ የዱቄት ግዢ ከ0.7 ሚሊዮን ወደ 0.5 ሚሊዮን ቶን ዝቅ ብሏል።

ለውጡ እንዴት መጣ?

አንዳንድ የሀገር ውስጥ የዱቄት ፋብሪካዎች ወደ ሥራ መመለሳቸው ሱዳን ከውጭ የምታስገባው ስንዴ በከፊል እንዲጨምር ሲያደርግ ከውጭ የሚገባ ዱቄት ላይ ፍላጎት ቀንሷል።

በዚህም ምክንያት ከሐምሌ እስከ ሚያዝያ ባለው ጊዜ ውስጥ፤ ሩሲያ ለአፍሪካ ከምትልከው አጠቃላይ ስንዴ ውስጥ የሱዳን ድርሻ ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረበት 4 በመቶ ወደ 10 በመቶ አድጓል። ይህም በሱዳን በኩል የፍላጎት መነቃቃት እና በአፍሪካ የስንዴ ገበያ ላይ ፉክክር መጨመሩ ያስከተለው ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0