በሐረሪ ክልል ለ250 አባወራዎች የሚሆን ሞዴል መንደር ሊገነባ ነው

ሰብስክራይብ
በሐረሪ ክልል ለ250 አባወራዎች የሚሆን ሞዴል መንደር ሊገነባ ነው

የሞዴል መንደሩ በገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮግራም አማካኝነት በቀጣይ ሁለት ወራት ውስጥ 250 አባወራዎችንና እማወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሆኖ እንደሚገነባ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ አስታውቀዋል።

በሞዴል መንደሩ ውስጥ የውኃ፣ የኃይል አቅርቦት እና ሌሎች አስፈላጊ መሠረተ-ልማቶች እንደሚሟሉም ገልፀዋል፡፡

‍ አርሶ አደሩ ፀጋውን ተጠቅሞ ኢኮኖሚውን እንዲያሳድግ ያግዛል የተባለውን የልማት ሥራ ስኬታማነት ለማረጋገጥ፤ ነዋሪዎችና ባለሥልጣናት በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ መቅረቡን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ተንቀሳቃሽ ምሥሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በሐረሪ ክልል የገጠር ኮሪደር ያደረጉትን ጉብኝት ያሳያል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0