በአፋር የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት የሚያጸና ተጨማሪ ሳይንሳዊ ጥናት ይፋ ሆነ

አፋር
አፋር  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.04.2026
ሰብስክራይብ
በአፋር የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት የሚያጸና ተጨማሪ ሳይንሳዊ ጥናት ይፋ ሆነ

በአፋር ስምጥ ሸለቆ መካከለኛው አዋሽ "ሀሊቢ" በተባለ ስፍራ 100 ሺህ ዓመታት በፊት ይኖሩ የነበሩ የጥንታዊ ሆሞ ሳፒየንስ ቅሪተ አካላት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች እና የእንስሳት ቅሪቶች ተገኝተዋል፡፡

ግኝቱ ዓለም አቀፍ እውቅና ባለው የሳይንስ መጽሔት ታትሟል። ጥናቱ በአፍሪካ የሰው ዘር ታሪክ ውስጥ ከ900 ሺህ እስከ 200 ሺህ ዓመታት የነበረውን ሰፊ የመረጃ ክፍተት የሚሞሉ አዳዲስ መረጃዎችን ይዟል ተብሏል።

ይህ ጥናት የተጀመረው እ.እ.አ በ1981 ሲሆን ላለፉት 45 ዓመታት ሲካሄድ መቆየቱን እና አሁንም በመካሄድ ላይ መሆኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶክተር በርሄ አስፋው ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0