ሃንጋሪ የሩሲያን የኢነርጂ አቅርቦት እንደምታስቀጥል ተመራጩ ጠቅላይ ሚኒስት ተናገሩ

ሰብስክራይብ
ሃንጋሪ የሩሲያን የኢነርጂ አቅርቦት እንደምታስቀጥል ተመራጩ ጠቅላይ ሚኒስት ተናገሩ

ሃንጋሪ የኢነርጂ አቅርቦት አማራጮቿን ለማስፋት ትሠራለች፣ ሆኖም ከሩሲያ የምታስገባውን አቅርቦት አታቋርጥM ሲሉ የቲስዛ (Tisza) ፓርቲ መሪ ፒተር ማግያር ተናግረዋል፡፡


“መልካምድርን መቀየር አንችልም። ሩሲያ እዚሁ ትቆያለች፤ ሃንጋሪ ባለችበት ትቆያለች” ያሉት ማግያር፤ ቡዳፔስት ርካሽ እና አስተማማኝ የኢነርጂ ምንጮችን ፍለጋ እንደምትቀጥል አፅንዖት ሰጥተዋል።


ማግያር፣ ዩክሬን ውስጥ ያለው ግጭት ካበቃ በኋላ በሩሲያ ላይ የተጣለው የአውሮፓ ሕብረት ማዕቀብ ሊነሳ እንደሚችል ተስፋቸውን ገልጸዋል። ይህም ወደፊት ለሚኖረው የኢነርጂ ፖሊሲ ይበልጥ ተግባራዊ አካሄድ መከተል እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0