በማንኛውም ሰበብ ወደ ሆርሙዝ የሚጠጋ የትኛውም የውጭ አገር ወታደራዊ መርከብ ‘ከባድ እርምጃ ይወሰድበታል’ - የኢራን አብዮታዊ ዘብ

በማንኛውም ሰበብ ወደ ሆርሙዝ የሚጠጋ የትኛውም የውጭ አገር ወታደራዊ መርከብ
በማንኛውም ሰበብ ወደ ሆርሙዝ የሚጠጋ የትኛውም የውጭ አገር ወታደራዊ መርከብ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.04.2026
ሰብስክራይብ
በማንኛውም ሰበብ ወደ ሆርሙዝ የሚጠጋ የትኛውም የውጭ አገር ወታደራዊ መርከብ ‘ከባድ እርምጃ ይወሰድበታል’ - የኢራን አብዮታዊ ዘብ

የሆርሙዝ ወሽመጥ “በተመጣጣኝ ቁጥጥር እና አስተዳደር ስር” እንደሚገኝ እና ለሲቪል መርከቦች “ልዩ ደንቦችን በሚያከብር መልኩ” ለትራንስፖርት ክፍት መሆኑን የኢራን አብዮታዊ ዘብ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል።

ይህ አቅርቦት ግን ወታደራዊ መርከቦችን አይመለከትም፤ እነዚህ መርከቦች “በማንኛውም ሰበብ” ወደ ባሕር ሰርጡ መቅረባቸው “እንደ ተኩስ አቁም ስምምነት ጥሰት ተቆጥሮ ከባድ እርምጃ ይወሰድባቸዋል” ሲል የኢራን አብዮታዊ ዘብ አስጠንቅቋል።

ይህ መግለጫ የወጣው፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ “ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ ለመግባት ወይም ለመውጣት የሚሞክሩ ማናቸውም መርከቦች” ላይ የባሕር ላይ እገዳ መጣሉን ካወጁ እና በአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ ተኩስ የሚከፍቱ የኢራን ኃይሎችን “ወደ ሲኦል እንሰዳቸዋለን!” በማለት ከዛቱ በኋላ ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0