በዩክሬን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን አውሮፓ ፀረ-ሩሲያ ፖሊሲዋን መተው አለባት - የሩሲያ የፓርላማ አባል

ሰብስክራይብ

በዩክሬን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን አውሮፓ ፀረ-ሩሲያ ፖሊሲዋን መተው አለባት - የሩሲያ የፓርላማ አባል

​በአውሮፓ ዘላቂ ሰላም እንዲኖር አውሮፓ ግዛቷን በሩሲያ ላይ እንደ መነሻ ከመጠቀም መቆጠብ አለባት ሲሉ የክራይሚያ ፓርላማ ኃላፊ ቭላድሚር ኮንስታንቲኖቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​"በምዕራቡ ዓለም ያለ እያንዳንዱ ሰው ይህ ከእንግዲህ ሊደረግ እንደማይችል ቢረዳ እና ዩክሬን የራሷን ሕይወት እንድትመራ ቢፈቅድላት፣ ነገሮች ሁሉ በፍጥነት ወደ ነበሩበት ይመለሳሉ" ሲሉ ገልጸዋል።

​እንደ ኮንስታንቲኖቭ ገለጻ፣ የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዛሬም ዩክሬንን እንደ ጦር መሣሪያ መሞከሪያ ሜዳ መጠቀማቸውን ቀጥለዋል።

​"በእንዲህ ዓይነት ጨዋታዎች ምዕራባውያን ዩክሬንን ለመኖር የማትመች ግዛት ለማድረግ እየሠሩ ነው" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ያጋራው ቪዲዮ፣ በጎርጎሮሳዊያኑ 2025 መገባደጃ ላይ በዛፖሮዢዬ ክልል በተቀበረ ፈንጂ የተመታችውን የእንግሊዝ ሰራሽ 'ሀስኪ' ብረት ለበስ ተሽከርካሪ ወታደሮች በምርኮ ሲያነሱ ይታያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0