የአፍሪካን አቅም ለመጠቀም የአፍሪካ ሕብረት መዋቅራዊ ለውጥ ሊደረግበት ይገባል - የኬንያ ፕሬዝዳንት

ሰብስክራይብ
የአፍሪካን አቅም ለመጠቀም የአፍሪካ ሕብረት መዋቅራዊ ለውጥ ሊደረግበት ይገባል - የኬንያ ፕሬዝዳንት

​ዊሊያም ሩቶ በሞምባሳ በተካሄደው የማሻሪኪ የትብብር ኮንፈረንስ ላይ እንደተናገሩት፣ የአፍሪካ ሕብረት ከአኅጉሪቱ ፍላጎቶች ጋር የተጣጣመ አይደለም።

እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ፣ ሕብረቱ ከአጣዳፊ ለውጦች ወደ ኋላ እንዳይቀር ተቋማቱ እና አካላቱ ወቅታዊ ፈተናዎችን ለማሸነፍ ብቁ ሆነው መገንባት አለባቸው።

​ፕሬዝዳንቱ አኅጉሪቱ ያላትን ከፍተኛ የተፈጥሮ ሀብት፣ ወጣት የሰው ኃይል እና እያደገ የመጣውን ገበያ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ሕብረቱ በአሁኑ ወቅት ለአኅጉሪቱ የበለጸገ መጻኢ እድል ማረጋገጥ እንደማይችል ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የድርጅቱን ዋና ዋና ድክመቶች እንደሚከተለው ዘርዝረዋል፡-

🟠 ደካማ ቅንጅት፣
🟠 ውሳኔ አሰጣጥ መዘግየት እና
🟠 የተቋማዊ ብቃት ማነስ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0